በታሪክ አጋጣሚ በሺዎች የምንቆጠር ኢትዮጵያዊያኖች ነፃ የትምህርት ዕድል እግኝተን በኩባ ሪፑብሊክ ለብዙ ጊዜ ትምርታችንን ስንከታተል ረጅም ዓመታቶችን እሳልፈናል ። በእሁኑ ሰአት በተለያዩ ምክንያቶች በአውሮፓና እንዲሁም በሌሎች የአለም ክፍሎች እንገኛለን ፤በዚህ የተነሳ ለረጅም ጊዜ በውስጣችን ስንመኘው የነበረውን ትልቅ ፍላጎት ባለፈው በሀምሌ ወር 2017 በሆላንድ ሀገር ኣውን ሊሆን ችሏል ።
በዚህ ለመጀመሪያ ጊዜ ባደረግነው የመገናኛ ፕሮግራም ላይ የተሰበሰበው ታዳሚም አንድ ጠንካራ የመረዳጃ ድርጅት መመስረት አማራጭ የሌለው ጉዳይ መሆኑን በሙሉ ድምፅ ሊወስን ችሏል። ይህም በአንድ መሪ ሐሳብ “መደራጀት ሐይል ነው” በማለትና በትክክል ጠንክረን ከተደራጀን አቅማችንን እና እውቀታችንንን ካበረከትን ለምንፈልጋቸው ግብአቶች በጥሩ ውጤት መድረስ እንችላለን ።